Teddy Afro - Mar Eske Tuwaf ( Fiqir Eske Meqabir) paroles de chanson

paroles de chanson Mar Eske Tuwaf ( Fiqir Eske Meqabir) - Teddy Afro



የጸበል ዳር እንኮይ ወንዝ ያወዛት ቅጠል
ተሸፈና ዋርካ ከልሏት የዛፍ ጠል
የት ነበር ያረኩት ቀፎየን ስል ኖሬ
ንብ ተከትዬ ባይ ጎጃም ኑራ ማሬ (ጎጃም ኖራለች ለካ)
ብራናዬ አንቺ የልጅነቴ ጓዴ
ተረሳሽ ወይ የሳት ዙሪያው ተረት በአንዴ
ብራናዬ አንቺ የልጅነቴ ቀለም
እኔ እንዳንቺ ያጠናሁት ፊደል የለም
ፍቅር የበዛበት፩ ዘልቆ ከማንኩሳ
መንናለች አሉኝ ብጫ ልብስ ለብሳ
ሸዋ ከሩፋኤል ስጠብቃት ኖሬ
ንቤ ገዳም ገብታ ጎጃም ኑራ ማሬ
ሲኖዳ ዮሐንስ ያመት ወዜን ይዤ
ጋማ ሽጦ ካሳ፪ ሸኝቶኝ ከወንዜ
መጥቼ ከሸዋ ስጠብቃት ኖሬ
ለካ ገዳም ገብታ ጎጃም ኑራ ማሬ
"ሀ" ብለህ ተው ድገም ሲሉኝ ንስሀ አባቴ
"ዋ" ብየ ተማርኩኝ አይ አለመስማቴ
ቀለም ወርቄ፫ ቢሆን የቅርቤ ጓደኛ
ፍቅር ለያዘው ሰው ከልካይ የለው ዳኛ
አሁን በማ ትኬ (ተክቼ) ይህ ልቤን ልካሰው
አንዴ በሷ ፍቅር የተረታሁኝ ሰው
የት እርቄስ ላገኝ ከፍቅሯ መሸሻ፬
እሷ ሆኖ ለኔ የአለም መጨረሻ
ማር ጧፍ ሁና
ማሬ ማሬ 4x
ጎጃም ኑራ ማሬ
ማር ጧፍ ሆኖ ገባ መቅደስ
ነዶ ለሊት ጸሎት ሊያደርስ
ዲማ ጊዮርጊስ ወይ ማንኩሳ
ያቺ ወንጌል፭ ብጫ ለብሳ
ከንግዲህማ ቆብ አስጥዬ
እንዳልወስዳት አባብዬ
ሰብልዬ ናት እማሆዬ
ሰብልዬ ናት እማሆዬ
ሰብል አለም በቢጫው ቀለም
ሰብል የአዳም ገባሽ ወይ ገዳም
ወይ ገዳም ገባሽ ወይ ገዳም
ኦሆ...
የጸበል ዳር እንኮይ ወንዝ ያወዛት ቅጠል
ተሸፍና ዋርካ ከልሏት የዛፍ ጠል
የት ነበር ያረኩት ቀፎየን ስል ኖሬ
ንብ ተከትዬ ባይ ጎጃም ኑራ ማሬ
ብራናዬ አንቺ የልጅነቴ ጓዴ
ተረሳሽ ወይ የሳት ዙሪያው ተረት በአንዴ
ብራናዬ አንቺ የልጅነቴ ቀለም
እኔ እንዳንቺ ያጠናሁት ፊደል የለም
ላሳደገኝ ደብር የሥለት ልጅ ሆኜ
ካሕን እንዴት ይፍታኝ ያንቺ እስረኛ ሆኜ
በጊዜ ተደፋ የቀለሙ ቀንዴ
የኔ ፊደል ማወቅ ካንቺ አዳነኝ እንዴ
ሳዋህድ ከኖርኩት ቅኔን ከደብተሬ
ተሽሎኝ ተገኘ ባለ አንዲሩ ገብሬ፮
ለካ ሰው አይድንም በደገመው መጽሐፍ
እንደሰም አቅልጦ ፍቅር ካረገው ጧፍ
ለካ ሰው አይድንም በኦሪቱ ገድል
ወንጌል ይዞ መጥቶ ፍቅር ካረገ ድል
ማር ሲገባ ገዳም ድንጋይ ተንተርሶ
ጧፉም እንደ መናኝ እዩት ቢጫ ለብሶ
ወንጌል መነኮሱ በልጅነታቸው
ማር እስከጧፍ ሆኖ አለም ቢነዳቸው
አንቺ የፍቅር ጥጌ ውድነሽ በጣሙን፯
መምጣቴ ነው በቃ እኔ አቃተኝ አሁን
አዲስ አለም፰ ሆነ ባንቺ ስለ ወጋየሁ፱
እድሌ ሆነና ባጣሽ ተሰቃየው
ማር ጧፍ ሁኔ
ማር ጧፍ ሁና
ማሬ ማሬ 4x
ጎጃም ኑራ ማሬ
ማር ጧፍ ሆኖ ገባ መቅደስ
ነዶ ለሊት ጸሎት ሊያደርስ
ዲማ ጊዮርጊስ ወይ ማንኩሳ
ያቺ ወንጌል ብጫ ለብሳ
ከንግዲህማ ቆብ አስጥዬ
እንዳልወስዳት አባብዬ
ሰብልዬ ናት እማሆዬ
ሰብልዬ ናት እማሆዬ
ሰብል አለም በቢጫው ቀለም
ሰብል የአዳም ገባሽ ወይ ገዳም
ወይ ገዳም ገባሽ ወይ ገዳም
ኦሆ...
ዘንግ ይዛ ማር ዘንግ ይዛ



Writer(s): Teddy Afro


Teddy Afro - Ethiopia
Album Ethiopia
date de sortie
02-05-2017




Attention! N'hésitez pas à laisser des commentaires.