Sami Dan - Outro текст песни

Текст песни Outro - Sami Dan



አንደኛው የዘመን ሰዉ
የመቶ ዐመት ታላቅ ኋለኛው
ባዶ እግሩን ሀገሩን ያቀና
በላብ በደሙ የመሬቱን ድንበር የሳለው
አምላኩ ፍቃድ የሚኖረው በፆም በፀሎቱ ሠማይን የሚቀደው
ጠና ይስጥልኝ ይላል ወዳጁን ሲያገኘው
መልካሙን ብቻ ነው የሚመኘው
የሰው ስሜትን ነዉ የለበሰው
ደሙ ትኩስ ለጠላቱ ሀገር ይጨሳል ሲቆጣ ስሜቱ
ዐይኑ ፈጦ አፍሮ ፀጉሩ አንበሳን መስሎ ከነምንሽሩ
ውስጡ ደሞ አለ ትህትና ዛሬን የሚያስንቅ ዛሬን የሚያስቀና
ቤትማ የእግዜር ነው ብሎ መኝታ ለቆ ከመደብ ያድራል መሬት ወድቆ
የሰው ልክ የሰው መልካም ስብእናው አይለካም
አሱን መስሎ እራሱን ቀርፆ ባህሪውን ስሎ
ከወገኑ ከሚወደው እንደ ወጉ እንደ ቀዬው
ሳይማረጥ ዘር ሳይቆጥር ኖሮ ተቻችሎ
የአባት አባት የሀገር አድባር የአዛውንቱ ፍቅራቸውን ምርቃቱን በረከቱን ምክሩን ተቀብሎ
ፈጣሪውን አከበረ በሰው ልጅ ላይ የቆጠረ የሠማዩ በምድር ላይ ሊፈታ ሰው በአምላኩ ብሎ
ግን ዛሬ በህይወት የለም ከአፈር በታች ውሎ
የሶስት ዘመን ሰው ቅድመ አያት እኔ የልጅ ልጅ
ሁለተኛው እኔ ነኝ የዚ ዘመን ነኝ
ከአንደኛው የተመዘዝኩት
ግን ተለወጥኩ መልሼ እራሱን የምወቅሰው
ታሪኩን የማራክሰው
ኋላ ቀር ነህ እለዋለሁ
ምን ተውክልኝ እለዋለሁ
ሰዉነቱን አረክሳለሁ
የሰራውን አፈርሳለሁ
ከአፈሩ በታች ገብቼ
ሰላም አረፍቱን ነስቼ
በነገር ቢላ ስጠቀጥቀው
እሱ ግን አያወጋኝም ሄድዋል
መልስም የለው
እሱ ግን መልስም የለው
ከወንድሜ ጋር ሰላም የለኝም
መንገዴ ሁሉ የጠፋብኝን
Technology የበዛብኝ
በቸኝነት የሚያጠቃኝ
ትልቅ ሀገረ ተረክቤ ትንሽ ሆኜ ጠቦ ሃሳቤ
ከፋፍዬ አሳነስኳት መላወሻም አሳጣኋት
የኔ ስልጣኔ ሆነ መጥኔ
የሶስት ዘመን ሰው ቅድመ አያት እኔ የልጅ ልጅ
የሶስተኛ ዘመንን ሰው ፈራሁት
ከኔ ይብሳል እሱን ፈራሁት
ታሪኬን ሁሉ እየበረበረ
የተፃፈውን እየመነዘረ
ሀገር እንደቀማሁት ሲያዉቅ ደነገጠ
ንዴቱ ሁሉ ምድርን አግሎ አቀለጠ
በጣም ጭሶ እርር ብሎ እሳት እያናፋ
ገላ አጥነትን የሚሰብር ቃላት እየተፋ
ከምድር በታች ወድቄ አፈር ቢጫነኝም
ያረኩትን አውቃለሁ እና እረፍትስ የለኝም
ሀገር የለው ወገን የለው ከሜዳ በትኜ
አረኩት ሆደ ባሻ ታሪኩን አጥፍቼ
ከኔ የባሰ አውሬነቱ ከውስጡ ቢወጣም
ጥፋቱም አይመዘን ሀዘኑ ቅጥ አጣ




Sami Dan - Sibet
Альбом Sibet
дата релиза
01-09-2021




Внимание! Не стесняйтесь оставлять отзывы.